2017-12-28 10:09:00

የኢትዮጲያን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ፣ ከኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ጳጳሳት ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ


+በስመ አብ፣ ወወልድ፣ ወመንፈስ ቅዱሰ፣ አሀዱ አምላክ፡፡ አሜን፡፡

አምላክ ሆይ ሕዝብህን አድን፣ የአንተ የሆኑትንም ባርክ፣

እረኛቸውም ሁን፣ ለዘለዓለም ተንከባከባቸው። መዝ.፳፰፣፱

 

 

ስለሀገራችንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ፣

ከኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ጳጳሳት ጉባኤ የተሰጠ መግለጫ፡

 

 

ለመላው ካቶሊካውያንና በጎፊቃድ ላላቸው ኢትዮጵያውያን ሁሉ የእግዚአብሔርር ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡

እኛ የኢትዮጵያ ካቶሊካውያን ጳጳሳት ጉባኤ አባላት በዚህ ሳምንት በሚጠናቀቀው በ43ኛው መደበኛ ጉባኤችን ስለአገራችን ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ ከገዳማውያን፣ ገዳማውያት፣ ካህናት እና ምእመናን በያሉበት በቅዳሴ ጸሎት ስናደርስ ሰንብተን ዛሬ የሚከትለው መልእክታችን ለማስተላለፍ ወደናል።

የዚህን መግለጫ ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

ከሁሉም በፊት በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት በጠፋው ክቡር የሰው ሕይወት የተሰማንን መሪሪ ሃዘን እየገለጽን የሞቱ ወገኖቻችንን ቸሩ እግዚአብሔር አምላክ በመንግሥተ ሰማይ በምህረቱ እንድቀበላቸው፣ ለቤተ ሰቦቻቸውም መጽናናትን እንዲሰጣቸው ጸሎታችንን እንቀጥላለን። እንደዚሁም በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ከየቀዬአቸው ለተፈናቀሉ ወገኖቻችንና ሀብት ንብረታቸው ለወደመባቸው ከልብ የመነጨ ሀዘናችን እንገልጻለን፡፡  

የአገራችን የኢትዮጵያ ሕዝቦች በብዝኃነት ውስጥ ያለውን አብሮ ተከባብሮ፣ ተባብሮ የመኖርን ምስጥር  ብቻ ሳይሆን ይህ ከእግዚአብሔር የተስጠ ድንቅ የሆነ ጸጋ በውጭ ኃይሎች እንዳይበርዝ በጋራ በመከላከል የነጻነት ተምሳሌት በመሆን እንድንጠራ አድርገዋል።  ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን፡ ይህ መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ እሴቶቻን አደጋ ላይ የሚጥል ፈተናዎች እያተጋረጡብን መጥተዋል። ቀጠናችን ዘርፈ ብዙ በሆኑ ምክንያቶች ቢሆንም ግን በብሔረተኝነት የሚገለጹ በመንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ማንነታችን የሚፈታትኑ  ግጭቶች እየተከሰቱ ናቸው። በነዚህ ግጭቶች ምክንያት በርካታ ወገኖችን ለህልፈተ ሕይወት፣ የተረፉትን ደግሞ ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ሆኖዋል።

እንደሚታወቀው፡ በምስራቅ አፍርቃ የሚገኙ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፡ ለረጂም ዘመናት ልዩነታቸውን የአንድነት ምንጭ አድርገ፡ በሰላምና ባንድነት፣ በመደጋገፍና በፍቅር ሲኖሩ ቆይተዋል፡፡

 

ይህንንም ሁኔታ ስላሳሰበን በምሥራቅ አፍርቃ ጳጳሳት ጉባኤዎች ኅብረት አባል አገሮች ታንዛንያ፣ ማላዊ፣ዛምብያ፣ዩጋንዳ፣ኬንያ፣ ኢትዮጲያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኤርትራ፣ እና ታዛቢ አገሮች ጁቡቲ እና ሶማልያ ከ 2006 ዓ.ም. ጅምሮ ከእግዚአብሔር ስለተሰጠው የብዝኀነት፣ የሁሉም የሰውልጅ እኩል ክቡርነትና ሰላም ስናመሰግን፣ በሐጢአት ምክንያት ይህ ታላቅ ጸጋ እንዳይወሰድብንም ስንጸልይ ከርመናል።  ይህን መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የምስራቅ አፍርቃ ጳጳሳት ጉባኤን በሐምሌ ወር 2010 ለማካሄድ ዝግጅት በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ ጉባኤውን የሚያውጠነጥነው በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተመሠረተ ሕያው ብዝኃነት፣ሰብአዊ ክብርና ሰላማዊ አንድነት ለአመሰያ ሀገራት የሚል መሪ ላይ ነው፡፡ ይህን መሪ ቃል የመረጡበት ዋናው ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየታዩ ያሉ የብሔሬተኝነት ጉዳዮች ወደ ዘረኝነት ሊያመሩ የሚችሉ አዝማሚያዎች በመገንዘብ ነው፡፡

ይህንን አስከፊ ክስተት ለመቀልበስና፡ ኣከባቢውን ዳግም ወደ ነበረበት የሰላምና ተከባብሮ ኣብሮ የመኖር ቀጠና ለመመለስ፡ የካቶሊክ ቤተክርስትያን፡ ለቀጠናው ህዝብ በተለይም ለአገራችን ሕዝቦች እርቀ ሰላሙ፣ እንዲሁም ደግሞ ህብረቱ ተፋቅሮና ተከባብሮ የመኖር ጸጋ ተመልሶ እንዲመጣ በማድረግ ሂደት፡  የበኩሉዋን ነቢያዊና ሞራላዊ ሃላፊነት ትወጣ ዘንድ እንደሚገባት ትገነዘባለች፡፡ ይህንን ኣንገብጋቢ ተልእኮ ባ ግባቡ መወጣት ትችል ዘንድ ደግሞ፡ በሂደቱ የካቶሊክ ቤተክርስትያን፡ ሚናና ድርሻ ምንነትና ኣስፈላጊነት ላይ በጥልቀት መመርመርና ማሰላሰል ኣስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በዚህም ምክንያት፡ የምሥራቅ አፍርቃ ካቶሊክ ቤተክርስትያን የጳጳሳት ጉባኤዎች ህብረት ይህንን ጉባኤ ጠርቷል፣ በኢትዮጲያም እንዲካሄድ ምልአተ ጉባኤው ከአራት ዓመት ብፊት ወስነዋል፡፡ ጉባኤው በአራት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በጥልቀት እንደሚወያ ይጠበቃል፣ በአመዛኙ የትኩረት አቅጣጫ ሊሆኑ የሚችለው ጉዳዮች፤

በ19ኛው የኅብረቱ ጉባኤችን በእግዚአብሔር ላይ የተመሠረተ ሕያው ብዝኃነት፣ ሰብአዊ ክብርና ሰላማዊ አንድነት ለአመሰያ ሀገራበሚለው መሪ ቃል መሰረት፡ የቀጠናውን ሁኔታ በጥልቀት መመርመር፣








All the contents on this site are copyrighted ©.