2017-11-28 14:54:00

የር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በምያንማር እና በባንግላዲሽ የሚያደርጉትን 23ኛውን የሐዋሪያዊ ጉዞ በይፋ ጀመሩ።


የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ  በማያንማር (በርማ) እና በባንግላዲሽ ከኅዳር 17-23/2010 ዓ.ም. የሚያደርጉት 21ኛው ሐዋሪያዊ ጉብኝት መርሃግብር

 

VViaggio Apostolico del Santo Padre in Myanmar e Bangladesh
            (26 novembre - 2 dicembre 2017)

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች በዛሬው እለት ትኩረት ሰጥተን ወደ እናንት የምናደርሰው ዘገባ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በማያንማር (የቀደሞ ስሟ በርማ)እና በባንላዲሽ ከኃድር 17 እስከ ኅዳር 23/2010 ዓ.ም. ድረስ የሰላም ልዑክ በሚል መሪ ቃል የሚያደሩትን 21 ኛውን ሐዋሪያዊ ጉብኝት የተመለከቱ ዘገባዎችን በሰፊው ወደ እናንተ እናቀርባለን።

እሁድ ኅዳር 17/2010 ዓ.ም.

.

መነሻ

 

ሰዓት

ርቀት

መድረሻ

1

ከሮም ሊዮናርዶ ዳቪንቺ ዓለማቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ

 

በኢትዮጲያ የሰዓት  አቆጣጠር

ከምሽቱ 05፡40

8,584 ኪ.ሜ

የ10፡20 ደቂቃ በረራ

የማያማር ዋና ከተማ ያንጎን

በኢትዮጲያ የሰዓት አቆጣጠር ከጥዋቱ 4፡00

 

 

 

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በማያንማር እና በባንግላዲሽ ከኅዳር 17 እስከ ኅዳር 23/2010 የሚያደርጉትን ጉብኝት በትላንትናው እለት ማታ ጀመሩ።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በማያንማር እና በባንግላዲሽ ከኅዳር 17 እስከ ኅዳር 23/2010 የሚያደርጉትን ጉብኝት በትላንትናው እለት ማታ ጀምረዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ ይህንን 21ኛ ሐዋሪያዊ ጉብኝታቸውን ከመጀመራቸው በፊት እንደ ተለመደው ማንኛውንም ዓይነት ሐዋሪያዊ ጉብኝት ለማድረግ ከሮም ከተማ በሚወጡበት እና ሐዋሪያዊ ጉብኝታቸውን አጠናቀው በሚመለሱበት ወቅት በሮም ከተማ እምብርት ላይ በሚገኘው እና በአውሮፓ በማሪያም ስም ከተሰየሙት ባዚልካዎች መካከል በትልቅነቱ በሚታወቀው፣ በ18ኛው ክፍለ ዘመን ግንባታው እንደ ተጠናቀቀ በሚነገርለት በሳንታ ማሪያ ማጆሬ (Sanat Maria Maggiore) ባዚሊካ ተገኝተው ይህ ሐዋሪያዊ ጉብኝታቸው የሰመረ ይሆን ዘንድ፣ በሚጎበኝዋቸው ሀገራት ውስጥም ሳይቀር ሰላም እና ፍቅር ይስፈን ዘንድ ጉዞዋቸውን ለማሪያም በደራ በመስጠት የእንደ ሚጀምሩ፣ በተመሳሳይ መልኩም ጉብኝታቸውን አጠናቀው በሚመለሱበት ወቅትም ሳይቀር በዚሁ ቤተክርስቲያን በመገኘት ለእግዚኣብሔር ምስጋናን ያቀርባሉ፣ በዚህም መስረት በትላንትናው እለት አመሻሹ ላይ በዚሁ በሳንታ ማሪይ ማጆሬ ባዚሊካ ተገኝተው ጸልት አድርሰዋል።

ቅዱስነታቸው ባሳንታ ማሪያ ማጆሬ ባዚሊካ ተገኝተው ጸሎት ካደርሱ ቡኃላ በትላንትናው እለት በኢትዮጲያ የሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 5:40 ላይ በሮም ከተማ ከሚገኘው እና በ15ኛው ክፍለ ዘመን በኖረው የጌታን የመጨረሻ እራት እና ሞናሊዛን በመሳሰሉ ድንቅ በሆኑ ስዕሎቹ በሚታወቀው ብሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ ስም ከተሰየመው ዓለማቀፍ የአውሮፕላን ማርፊያ በመነሳት ጉዞዋቸውን ጀምረው 8584 ኪሎ መትሮችን በአየር ላይ አቋርተው የ10፡20 ደቂቃ ጉዞ ካደረጉ ቡኃላ በኢትዮጲያ የሰዓት አቆጣጠር ከጥዋቱ 4 ሰዓት ላይ በማያንማር በያንጎን ከተማ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የአየር ማርፊያ ጣቢያ በሰላም አርፈዋል።

ቅዱስነታቸው ወደ ምያንማር ባደርጉት የአይሮፕላን ጉዞ የበረራ የአየር ክልሎቻቸውን ያቋረጡባቸውን አህጉራት፥ ለኢጣሊያ ሪፓሊክ ርዕሰ ብሔር ሰርጆ ማታረላ፡ ለርዕሰ ብሔሩ እና ለኢጣሊያ ሕዝብ ጸሎት ማድረግ እንደ ሚቀጥሉ አረጋግጠው፣ ሕዝብን የጋራ ተጠቃሚ በሚያደርግ የጋራን ጥቅም ያማከል ተግባር እንደ ሚያከናውኑ በመሻት እን ተስፋ በማድረግ “በዚህ ወደ ምያንማር እና ወደ ባንግላደሽ የማደርገው በሁለቱ አህጉራት ለሚገኙት በቁጥር አናሳ የካቶሊክ ምዕመናን በእምነት ለማጽናት እና ለማበረታታት በማለም የሰላም ተጓዢ በመሆን በማደርገው ጉዞ ለእርስዎ ክቡር የኢጣሊያ ርዕሰ ብሔር ሰላምታዬን አቀርባለሁ” የሚል የተሌግራም መእክት እንዳስተላለፉ የቅድስት መንበር የዜናና ህኅትመት ክፍል መግለጫ ያስረዳል። በተመሳሳይ መልኩም የተሌግራም መልእክት የአየር በረራ ክልሎቻቸውን ላቋረጡባቸው ለክሮሺያ፣ ለቦስኒያና ኤርዘጎቪና፣ ለሞንተ ነግሮ፣ ለሰርቢያ፣ ለቡልጋርያ፣ ለቱርክ፣ ለጆሪጂያ፣ ለአዘርባጃን፣ ለቱርክ፣ ለአፍጋኒስታን፣ ለፓኪስታንና ለሕንድ መራሔ መንግሥታት ማስተላለፋቸውን ለመረዳት ተችሉዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.