2017-11-28 15:18:00

በቫቲካን እና በማያንማር መካከል ያላለው የዲፕሎማሲ ግንኙነት እና ትብብር


በቫቲካን እና በማያንማር መካከል ስላለው የዲፕሎማሲ ግንኙነት እና ትብብር

ቫቲካን እና ማያንማር ሪፖብልክ ኦፊሰሊያዊ የሆነ ግንኙነት የጀመሩት እንደ አውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር በግንቦት 4/2017 ዓ.ም. (ከሰባት ወራት በፊ ማለት ነው)በዚሁ ዓመት እንደ ተጀመረ ለመረዳት የተቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የቅድስት መንበርን በመወከል ከሀገሪቷ ጋር አስፈላጊውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እያደረገች የምትገኘው በአሁኑ ወቅት የታይላንድ፣ የካንቦዲያ እና የላዎስ የቅድስት መነበር አባሳደር በሆኑት በአቡነ ፖል ቻንግ ኢ ናም ለማያንማር የቫቲካን ልዩ ልዑክ በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በአሁኑ ወቅት በማያንማር በቁጥር አናሳ በሆኑ ሮሂንጋያ የሙስሊም ማኅበረሰብ ላይ በአገሪቱ የሚገኙ በአንድ አንድ አካራሪ የቡዳ እምነት ተከታዮች አማካይነት እየተፈጸ የሚገኘውን አሰቃቂ ጥቃት በማውገዝ የሰላም የኖቤል ተሸላሚ ለሆኑት እና በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር ለሆኑት ሳን ሱ ኪ በቁጥር አናሳ በሆኑት የሮሂንጋያ የሙስሊም ማኅበረሰቦች ላይ እየደረሰ ያለውን ጣቅት በማውገዝ ሰላም እና እርቅ እንዲፈጠር በተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወቃል።

በዚህም መሰረት ቅዱስነታቸው ባለፈው ግንቦት ወር ላይ የማያንማር ፕሬዚዳንት የሆኑትን ሳን ሱ ኪ ን በቫቲካን ጋብዘው በሁለቱ ሀገራት የወደ ፊት ግንኙነት እና በእነዚህ በቁጥር አናሳ የሆኑት የሮሂንጋያ የሙስሊም ማኅበረሰብ አባላት ላይ እየተቃጣ የሚገኘው ጥቃት ባስቸኳይ ይቆም ዘንድ እና ብሔራዊ እርቅ ይደረግ ዘንድ ይህንንም በተመለከተ በግል ተገናኝተው መወያየታቸው የሚታወስ ሲሆን በአንድ አንድ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ መድረሳቸውን እና ፕሬዚዳንት ሳን ሱ ኪም ቅዱስነታቸውን በኅዳር ወር ውስጥ ማያንማርን እንዲጎበኙ ጥሪ እንዳደረጉላቸው ያታወሳል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በማይንማር የሚያደርጉት በ21ኛ ሐዋሪያዊ ግብኝታቸው በአንድ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የተደረገ የመጀመሪያ ታሪካዊ ጉዞ ነው። በዚሁ ግቡኝታቸው ለቅዱስነታቸው ትላቁ ፈታና የሚሆንባቸው ነገር ቢኖር በአሁኑ ወቅት ከ600,000 ሺ በላይ ሰዎችን ለስደት እና ለመከራ የዳረገው በቁጥር አናሳ በሆኑት የሮሂንጋያ የሙስሊም ማሕበረሰቦች ላይ የተቃጣው ጥቃት ነው። ቅዱስነታቸው ይህንን ጥቃት በተደጋጋሚ አውግዘዋል። ነገር ግን አሁን አወዛጋቢ የሚሆነው ጉዳይ “ሮሂንጋያ” የሚለው የእነዚህ በቁጥር አናሳ የሆኑ የሙስሊም ማሕበረሰብ መጠሪያ መጠቀም እንደ ሌለባቸው የማያንማር ባለስልጣናት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱን አሳስበዋል። በሀገሪቷ የሚገኙ ብቸኛው ካርዲናልም ቅዱስነታቸው ይህንን የመጠሪያ ስም ባይጠቀሙ ይሻላ የሚል የበኩላቸውን አስተያየት ሰጥተዋል። ምክንያቱም “ሮሂናጋያ” የሚለው መጠሪያ የአንድ የማያንማር ጎሳ መጠሪያ ነው። ነገር ግን አብዛኛውን በማያንማር የሚኖሩ የቡዳ እምነት ተከታዮች እነዚህ በቁጥር አናሳ የሆኑ በማያንማር የሚኖሩ  የሙስሊም እምነት ተከታዮች በስደት ከባንግላዲሺ ወደ ማያንማር የገቡ በመሆናቸው የተነሳ ይህ “ሮሂንጋያ” የሚለው የማያንማር አንድ ጎሳ መጠሪያ ስም በመሆኑ፣ ለእነርሱ ይህ የመጠሪያ ስም አይገባቸውም በማለት እየሞገቱ ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት ቅዱስነታቸው ይህንን የመጠሪያ ስም ከተጠቀሙ በብዙኃኑ የቡዳ እምነት ተከታዮች ዘንድ ቁጣ ይቀሰቅሳል የሚል ስጋት ፈጥሩዋል። ነገር ግን ቀደም ባሉት ጊዜያት ቅዱስነታቸው “በወንድሞቻችን እና በእህቶቻችን የሮሂንጋያ ማሕበረሰብ ላይ የሚደርሰው ጥቃት እና ስደት ይብቃ!” ማለታቸውም ይታወስል።








All the contents on this site are copyrighted ©.