2017-08-14 15:38:00

ቅዱስ ኣባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ፥ በማርያም ውስጥ ትህትና የብርቱዎች ምግባር መሆኑ እንመለከታለን


ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ትዊተር በተሰየመው ማኅበራዊ መረብት ዘንድ ባለው @Pontifex የግል አድራሻቸው በኩል እንደ ወትሮው የሚያስተላልፉት ቃለ ምዕዳን በመቀጠል እሁድ እ.ኤ.አ. ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም.  (ነሐሴ 7 ቀን 2009 ዓ.ም.) በማርያም፥ ብርቱዎች መሆናቸው እንዲሰማቸው ሌሎችን ማሰቃየት ሳይሆን ሰብአዊነት ደግነትና ትህትና የብርቱዎች ምግባር መሆኑ እናስተውላለን፡ እንዳሉ የቅድስት መንበር የዜናን ኅትመት ክፍል መግለጫ አመለከተ።

ቅዱስ አባታችን ያስተላለፉት ቃል የወንጌል ሃሴት በሚል ራስ ሥር በደረሱት ሐዋርያዊ ምዕዳን እንዲሁም ባለፈው እ.ኤ.አ. 2016  ግንቦት ወር በፖርቱጋል ዝክረ 100ኛው ዓመት ግልጸተ ማርያም በፋጢማ ምክንያት በቅድስተ ማርያም ዘፋጢማ ቅዱስ ሥፍራ ወደ ሚገኘው የግልጸተ ማርያም ቤተ ጸሎት መንፈሳዊ ንግደት ባከናወኑበት ወቅት አስተላልፈዉት የነበረውን መልእክት አስተንፍሶ ያደረግ መሆኑ የገለጠው የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል መግለጫ አክሎ፡ ቅዱስነታቸው ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. በግልጸተ ማርያም ቤተ ጸሎት ተገኝተው፥ ከክርስቶስና ከማርያም ጋር እኛ በእግዚአብሔር ዘንድ እንሆናለን፡ ክርስቲያን ለመሆን ከፈለግን ማርያማውያን መሆን ይገባናል። ማለትም ማርያምንና ኢየሱስን የሚያስተሳስረው ወደ ኢየሱስ የሚመራን መንገድ የሚከፍት አስፈላጊው ህያው እና የእግዚአብሔር ኣሳቢነት የሚያረጋግጥ በመካከላቸው ያለው ግኑኝነት እውቅና መስጠት ይገባናል እንዳሉ በማስታወስ ይጠቁማል።

ቅዱስነታቸው በግልጸተ ማርያም ዘፋጢማ ቤተ ጸሎት፥ ማርያም፥ የመንፈሳዊ ሕይወት መምህር፥ ኢየሱስን በዚያ አስጨናቂ በሆነው በመስቀል መንገድ ለእኛ አብነት ለመሆን የተከተለች ቀዳሜ የእርሱ ተከታይ ነች፡ “ዘወትር በሁሉምና በማንኛውም ሁኔታ ስላመነች ብጽእት ነች፡ (ሉቃስ 1,42,45 ተመል.)። ወንጌላዊ ሓሴት ሐዋርያዊ ምዕዳን፥ “በየትኛውም ጊዜና ሁነት ማርያም ስንመለከትና የዋህነትና አሳቢነት ግብታዊ ኃይል እንዳለው ወደ ማመን ከፍ እንላለን፥ ትሕትና የዋህነት ኃይለ ልዕልናውንና የገዛ ኃይሉን ለማሳየት ሌሎችን ለመጉዳት ለሚል የሚሻው እንደሚመለከተው ድካምነት ሳይሆን የብርቱዎች መልካም ምግባር ነው፡ ይኽ የፍትህና የየዋህነት አስተንትኖ እና ወደ ሌሎች የማቅናት ሂደትም ነው፡ (ሓዋርያዊ ምዕዳን፥ ወንጌላዊ ሐሴት, 288 ቁጥር ተመል.)። እያንዳንዳችን በማርያም እና ከማርያም ጋር የዚያ ዘወትር ሁሉንም የሚምር የእግዚአብሔር ምሕረት ትእምርትና ምስጢር ይሁን እንዳሉ የቅድስት መንበር የዜናና ኅትመት ክፍል መግለጫ በማስታወስ ያመለክታል።








All the contents on this site are copyrighted ©.