የሐምሌ 23/2009 ዓ.ም. እለተ ሰንበት የወንጌል አስተንትኖ
የተወደዳችህ የእግዚኣብሔር ቤተሰቦች እና በጎ ፈቃድ ያላችሁ!
ዳዊት በመዝሙሩ “እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ እዩም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው” ይላል። እንደ የተግባራችን ሳይሆን በምሕረቱና በቸርነቱ የሚጎበኘን እግዚኣብሔር አምላክችን ቅዱስ ስሙ የተመሰገነ ይሁን። በዛሬው እለተ ሰንበት ለስተንትኖ ይሆነን ዘንድ ቤተክርስቲያናችን የሰጠችን የእግዚኣብሔር ቃል በቀዳሚነት የተወሰደው ሐዋሪያው ጳውሎስ ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች ከጻፈው ከሁለተኛ መልእክቱ 9:1-15 ላይ ያለው ሲሆን ይህም ለክርስቲያኖች ስለተደረገው መዋጮ የሚያመልክትና ክርስቲያኖች ለቤተክርስቲያን ወይም ሌሎች በችግር ላይ የሚገኙ ክርስቲያን ወንድሞቻቸውን በግድ ሳይሆን በፈቃደኝነት ሊረዱ ይገባል የሚለውን የሐዋሪያው ጳውሎስን መልእክት የያዘ ነው።
የእዚህን ዜና ሙሉ ይዘት ከዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!
በዛሬው እለተ ሰንበት በሁለተኛነት ለአስተንትኖ የተሰጠን የእግዚኣብሔር ቃል የተወስደው 1 ጴጥሮስ 3:15-22 ያለው ሲሆን በዚህም መልእክት “ እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ!” በማለት ሐዋሪያው ጴጥሮስ ዛሬ ለእኛ ጥሪ ያቀርባል።
የዛሬው ቅዱስ ወንጌል ከማቴዎስ ወንጌል 24፡36-51 የተወሰደ ሲሆን ይህም “ጌታ የሚመጣበት ጊዜ ስለማይታወቅ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ” በሚል ጭብጥ ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን ክርስቲያኖች ሁሉ እግዚኣብሔር መቼ እና እንዴት እንደሚጠራን ስለማንውቅ ተዘጋጅተን ምኖር ይኖርብናል በማለት ለእኛ ማሳሰብያ ያቀርባል።
ነቅቶ መጠበቅ
ባለንበት ዘመን የክርስቶስን በቶሎ የመምጣትን ወይም የዓለም ፍፃሜ እንደደረሰ የሚናገሩ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ በተለይም የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 24 ላይ ያለውን መሰረት በማድረግ፣ የተጠቀሱትን ምልክቶች በዋቢነት በመውሰድ ለምሳሌ የጥፋት ውኃ፣ ሁለት ሴቶች በወፍጮ ይፈጫሉ፤ አንዲቱ ትወሰዳለች አንዲቱም ትቀራለች የሚሉትን እና የመሳሰሉትን ምልክቶች በመጥቀስ ሌሎችን ሲያስቱ ይታያል፡፡
እንደ ክርስቲያን ልናስተውላቸው የሚገቡን ነገሮች አሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ የሚከተሰቱት ሰው ሰራሽ አደጋዎች ከሰው ልጅ የአእምሮ እድገት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ነገሮች ሲሆኑ የተፈጥሮ አደጋዎች ለምሳሌም የመሬት መንቀጥቀጥ የመሳሰሉ አደጋዎች ግን ድሮም የነበሩ፣ ዛሬም ያሉ፣ ወደፊትም የሚኖሩ ናቸው፡፡ በብሉይ ኪዳን በተለይም በኖኅ ዘመን የሰው ክፋት በጣም ታላቅ እንደነበረና እግዚአብሔርም በዚያ እንዳዘነ ስለዚህ ሰዎችና ፍጥረታት ሁሉ በምድር ላይ ታላቅ ጐርፍ በመላክ ለማጥፋት ወሰነ፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው እሱም ኖኅ ብቻ ጻድቅ ሆኖ ተገኘ፡፡ በእግዚአብሔር ዘንድ ተወዳጅ ስለነበር እግዚአብሔር ኖኅን አንድ ትልቅ መርከብ ስራ በማለት እርሱንና ቤተሰቡን በመርከብ ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ አዳነ፡፡ የቀሩት ሰዎች በዓለም ይደሰቱ ነበር፣ የእግዚአብሔርን ፍርድ አልፈሩም፡፡ ኖኅም ትልቁን መርከብ በመስራቱ ሳቁበት ተሳለቁበት፡፡ ጐርፍ ይመጣል የሚል እምነት ስላልነበራቸው ጨርሰው አልተዘጋጁም ነበርና ሁሉም ጠፉ ይለናል በኦሪት ዘፍጥረት 7፡6-24፡፡ እያንዳንዳችን ነቅተን የምንጠብቀው እንዴት ነው? ምን ዓይነት ተግባራትን በመሥራት ነው ንቅተን መጠበቅ የሚኖርብን? ክርስቶስ በድንገት በሚመጣበት ወቅት ምን ዓይነት ተግባራትን እየፈጸምን ሊያገኘን ይገባል? የሚሉትን ጥያቀዎች ዛሬ ማንሳት ይኖርብናል። እንደ ክርስቶስ ተከታዮች ልንተገብራቸው የሚገቡን ክርስቲያናዊ ተግባሮች አሉ እነርሱም በእየ እለቱ ሥጋዊ የምሕረት ተግባራትን ማከናውን ይጠበቅብናል ማለት ነው።
እነዚህ ሥጋዊ/አካላዊ የምሕረት ተግባራት ጠንቅቀን የምናውቃቸው ነገር ግን አብዝተን የምንዘነጋቸው መሰረታቸውን በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 25: 31 ጀምሮ በጠጠቀሰው የኢየሱስ አስተምህሮ ላይ የተመረኮዘ ሲሆን ይህም በዓለም መጨረሻ የሚሆነውን የፍርድ ሂደት የሚያመልክትና “ኢየሱስ በመላእክቱ ታጅቦ በፍርድ ወንበር ላይ በመቀመጥ፣ እረኛው በጎችን ከፍዬሎች እንደሚለይ እርሱም ሕዝቦችን ይለያል፣ በጎቹን በቀኙ ፍዬሎቹን ደግሞ በግራው ያቆማቸዋል” እንደ ሚለው በመጨረሻው ቀን በኢየሱስ ፊት በምንቆምበት ወቅት ለሚያቀርብልን ጥያቄዎች በድፍረት በቂ የሆነ ምላሽ መስጠት እንድንችል እና ከፍየሎቹ ተርታ ሳይሆን ገበጎቹ ጎራ መሰለፍ እድንችል የሚያግዙን ተግባራትን መፈጸም ይገባል። እነዚህ ሥጋዊ/አካላዊ የምሕረት ተግባራት እነማን ናቸው?
ደም መለግስ
በማይድን በሽታዎች የሚሰቃዩትን ሰዎች ወደ አሉበት ሥፍራ ሄዶ ማጫወት፣ ማዋራት፣ ስቃያቸውን ለጊዜውም ቢሆን እንዲረሱ ማድረግ ያስፈልጋል።
በአከባቢያችን የሚገኙትን የእድሜ ባለዘጎችን መጎብኘት ያስፈለጋል።
ምግብ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ካሉ፣ መድኋኒት የሚፈልጉ ካሉ የመሳሰሉትን እርዳታዎችን ማድረግ ይጠበቃል።
6 የታሰረን መጐብኘት፡- ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች፣ አውቀውም ሆነ ሳያውቁ በሰሩት ጥሩ ባልሆነ ተግባር ወይም በግፍ ዘብጥያ ወይም ወኅኒ ሊገቡ ወይም ሊታሰሩ ይችላሉ፡፡ የሚታሰሩ ሁሉ ጥፋተኞች ናቸው ማለት ግን ስህተት ነው፡፡ ምክንያቱም ያለበደላቸው የሚታሰሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ሐዋርያትም ለምሳሌ ጳውሎስና ሲላስ የኢየሱስን ስም ስለጠሩ ብዙ ግዜ ታስረዋል፡፡ /የሐ.ሥራ 16፡ 23-4ዐ/ የዕብራውያን ፀሐፊ “እስረኞችን አስቡ ይለናል” አስቡ ሲለን ሄደን መጠየቅና መገዝን ያጠቃልላል፡፡ ነቅቶ መጠበቅ ማለት ይህ ነው፡፡
7. የሞተን ምቅበር (መ. ጦቢት 1.17-19)
የቀብር ሥነ-ሥረዓትን በምንታደምበት ወቅት ሁሉ እንዚህ በሐዘን የተጎዱ ሰዎችን በዚህ ወሳኝ እና አስቸጋሪ በሆነ ወቅት መጽናናትና እና ብርታትን የመግለጫ ምልክት ነው። እንዲሁም በቀብር ሥነሥረዓት ላይ ተገኝተን ጸሎይ በምናደርግበት ወቅት ለሕይወት ያለንን ክብር እንገልጻለን ። ሐዘን የሰውን ልብ የሚሰብር ጉዳይ ነው። ሐዘን ሰው ተስፋ እንዲቆርጥ የሚያደርግ ነገር ነው። የሰውን ሐዘን ልንጋራ ያስፈልጋል። ሞት ለሁላችንም የማይቀር እጣ ፈንታ ቢሆንም ቅሉ በሞት የተለዩንን ወዳጅ ዘመዶቻችንን ማጣት ቀላል ነገር ባለመሆኑ የተነሳ በሐዘን የተጎዱ ሰዎችን ማጽናናት ያስፈልጋል።
የተወደዳችሁ የእግዚኣብሔር ቤተሰቦች እና በጎ ፈቃድ ያላችሁ በሙሉ!
በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ላይ እንደ ተጠቀሰው ኢየሱስ “ጊዜውን እና ወቅቱን ሰለማታውቁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ” ይለናል። ከላይ የተጠቀሱትን መልካም ነገሮችን በመፈጸም ነቅተን እርሱን መጠበቅ እንችል ዘንድ የእግዚኣብሔር ጸጋ እና ድጋፍ ያስፈልጋል። ሁልጊዜ ነቅተን መልካም ተግባራትን እየፈጸምን ያገኘን ዘንድ የክርስቲያኖች ረዳት የሆነችሁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያ በአማልጅነቷ ትርዳን። አሜን!
(አባ መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ)
All the contents on this site are copyrighted ©. |