2017-01-12 15:22:00

ከቫቲካም ሬዲዮ የአማሪኛ የስርጭት ክፍል የተላለፈው የረዕቡ የጥር 03/2009 ዓ.ም. ዜና።


ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ 2/2009 ዓ.ም. በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት ካህናት ደናግላን እና ምዕመናን በተገኙበት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ወቅት ባሰሙት ስብከት እንደ ገለጹት ሁለተኛው የኢየሱስ ስልጣን መገለጫ ባሕሪ የነበረው ለሕዝቡ ያለው ቅርበት ነው ማለታቸው ተገልጸ።

የእዚህን ዜና ሙሉ ይዘት ከእዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ።

ለሕዝብ ቅርብ መሆን ያለነን ስልጣን ያረጋግጣል ያሉት ቅዱስነታቸው ይህም ኢየሱስ ለሕዝቡ የነበረው ቅርበት ከፈሪሳዊያን በተሻለ ሁኔታ ስልጣኑን ሊያረጋግጥለት ችሎ እንደ ነበር በመጥቀስ ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው “ኢየሱስ በምንም ዓይነት ሁኔታ ለምጻሞችን እና በሽተኞችን መንካት በፍጹም ተጸይፎ” አያውቅም ነበር ብለዋል።

ነገር ግን በተቃራኒው ፈሪሳዊያን “ድኸ እና ያልተማሩ ሰዎችን ይንቁ ነበረ” በማለት ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው በየ አደባባዩ ምርጥ የሚባሉ ልብሶችን በመልበስ መዘዋወር ይወዱ እንደ ነበረም ጭምረው ገልጸዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.