2016-11-26 10:12:00

ከቫቲካን ሬዲዮ የአማሪኛ የስርጭት ክፍል የተላለፈው የአርብ የኅዳር 16/2009 ዓ.ም. ዜና።


ቅዱስ አባታችን ፍራንቸስኮ በትላንትናው እለት ማለትም በኅዳር 15/2009 ዓ.ም. በቅድት ማርታ የጸሎት ቤት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ባሰሙት ስብከት ሙሳን ገንዘብን እንደ ማምለክ ስለሚቆጠርና ሌሎችን የሚበዘብዝ ሴራ በመሆኑ እግዚኣብሔን እንደ መሳደብ ይቆጠራል ማለታቸው ተገለጸ።

በእለቱ የተነበቡት ምንባባት ትኩረታቸውን በዓለም ፍጻሜ ስለሚከሰቱ ነገሮች፣ ስለመጨረሻ ፍርድና  ታማኝ አገልጋይ የሆኑ ሰዎችን እግዚኣብሔር እነርሱን እንደ ሚበጅ የሚገልጽ እንደ ነበር የታወቀ ሲሆን ቅዱስንታቸውም በእዚህ ዙሪያ ባጠነጠነ ስብከታቸው እንደ ገለጹት ታላቂቷ ባቢሎን የፈራረሰቺው በሙሳን መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።

ሙስና እግዚኣብሔርን እየተሳደቡ እንደ መኖር ይቆጠራል ብለው በአጽኖት በመግለጽ ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ይህም ቃል ዓለማዊ ኑሮን ስሚገልጽ የባቢሎኖች ቋንቋ ነው ብለዋል። ሙስና አምላክ በሌለበት ቦታ አምላክን እንደ መሳደብ ይቆጠራል በማለት ስብከታቸውን የቅጠሉት ቅዱስነታቸው በዛ ስፍራ የሚኘው እንደ አምላክ የሚቆጠረው ገንዘብና በሌሎች ላይ የሚደረግ ብዝበዛ ነው ማለታቸውም ተገልጹዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.