2013-12-18 16:12:26

ላምፔዱዛ፦ የስደተኞች ሁኔታ


RealAudioMP3 በኢጣሊያ የስደተኞችና ተፈናቃዮች መጠለያ ሠፈር በተለይ ደግሞ በላምፔዱዛ ያለው ሁኔታ በቅርብ የተመለከተው የተበበሩት መንግሥታት የስደተኞችና ተፈናቃዮች የበላይ ድርገት የስደተኞች መጠለያው ሠፈር እርሱም የመጀመሪያ የማስናገጃ ሠፈርና ቀጥሎም የስድተኞች የጥገኝነት ጥያቄ መልስ የሚጠባበቁበት ተብሎ ቆይታ የሚያደረጉበት መጠለያ ሠፈር የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞችና የተፈናቃዮች ደንብ የሚከተልና የሚያከብር እንዲሆን ለኢጣሊያ መንግሥት ጥያቄ አቅርበዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የላፔዱዛው የስደተኞች ማስተናገጃ ማእከል ማስተናገጃ እንጂ መጠለያ ሠፈር አለ መሆኑ በተደጋጋሚ ሁኔታውን በቅርቡ የተከታተለው ይኽ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለኢጣሊያ መንግሥት አሳውቆ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፣ ስለዚህ የላፔዱዛው ማሰተናገጃው ሠፈር 850 ሰዎች ለማድተናገድ የሚችል ሆኖ እያለ በአሁኑ ሰዓት በስደተኛ ብዛት ተጨናንቆ ያያል፣ ይኽ ደግሞ ለስደተኛውም ሆነ በማእከል አገልግሎት ለሚሰጡት አመች አለ መሆኑ የተብበሩት መንግሥታት ድርጅት በማብራራት፣ ስደተኞቹ ያቀረቡት ጥያቄ አሁንም ከብዙ ወራት በኃላም ግና መልስ ሳያገኝ ወይንም ስደተኛው ገና ጥያቄው ሳያቀርብ እዛው እንዲቆይ ማድረግ ያለ ዘገምተኛው አሰራር የስድተኛው በስድተኛው ላይ የተለያየ ችግር እያስከተለ መሆኑ የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞችና ተፈናቃዮች የበላይ ድርገት ለኢጣሊያ መንግሥት የአስቸኳይ መልስ ጥሪ አቅርበዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.