2013-03-04 14:28:05

የቅድስት መንበር የዜናና ማኅተም ክፍል መግለጫ


RealAudioMP3 በቅዱስ ጴጥሮስ ባሲሊካ በጸሎት ዙሪያ የጠመረች ኃያው ቤተ ክርስቲያንን የሚያረጋግጥ በቅዱስ ቁርባን ፊት በዚህ የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ መንበር ክፍት በሆነበት ወቅት ስለ ቅዱስት ቤተ ክርስቲያንና የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ ለመምረጥ ብፁዓን ካርዲናሎች ለሚያደርጉት ዝግ ቅዱስ ጉባኤ ሃሳብ ያደረገ በቅዱስ ቁርባን ፊት ቀጣይ የአስተንትኖና የጸሎት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ መሆኑ የቅድስት መንበር የዜናና ማኅተም ክፍል ተጠሪ የቫቲካን ረዲዮ ዋና አስተዳዳሪ አባ ፈደሪኮ ሎምባርዲ ትላትና በቅድስት መንበር የዜናና ማኅተም ክልፍ ሕንፃ በሚገኘው የጉባኤ አዳራሽ ለተገኙት የውስጥና የውጭ አገር ጋዜጠኖች በሰጥት ጋዜጣው መግለጫ በማብራራት በቅዱስ ጴርጥሮስ ባሲሊካ ከቅትር በኋላ ከሚቀርበው መሥዋዕተ ቅዳሴ ቀጥሎ ልዩ ስለ ብፁዓን ካርዲናሎች ጸሎት እንደሚደረግና ይኽም የቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ ለመምረጥ የሚያደረጉት ዝግ ቅዱስ ጉባኤ ላይ ያተኮረ መሆኑ አብራርተዋል።
ሁሉም ሰማንያ ዓመት ዕድሜ ያልሞላቸው ብፁዓን ካርዲናሎች ቅዱስ አባታችንን ለመረጥ እንደሚሰበሰቡና ዛሬ በአገረ ቫቲካን በሚገኘው አዲስ የሲኖዶስ አዳራሽ የመጀመሪያው ለቅዱስ ጴጥሮስ ተከታይ ምርጫ በሲስቲና ቤተ ጸሎት ለሚደረገው ዝግ ስብሰባ ቅድመ ዝግጅት የብፁዓን ካርዲናሎች አፈ ጉባኤ ብፁዕ ካርዲናል አንጀሎ ሶዳኖ የጠሩት ጉባኤ መካሄዱ ተገልጠዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.