2009-07-20 14:07:49

ዴሞክራሲያዊት ሬፓብሊክ ኮንጎ


በዴሞክራሲያዊት ሬፓብሊክ ኮንጎ ርእሰ ከተማ ኪንሻሳ የሚገኙት የካቶሊክ ተቋሞች ባንድ ላይ በመጠራነፍ የኮንጎ የካቶሊክ መንበረ ጥበብ ለመሆን መብቃታቸው ተገለጠ። የአገሪቱ ብጹዓን ጳጳሳት ጉባኤ ሊቀ መንበር RealAudioMP3 የተቋቋመው የኮንጎ የካቶሊክ መንበረ ጥበብ ዋና አስተዳዳሪ የሹምቤ ሊቀ ጳጵሳት ብፁዕ ኣቡነ ኒኮላስ ድጆሞ ሎላ የተቋቋመው መንበረ ጥበብ እቅድ በተለያዩ ዘፈሮች ዜጎችን በማነጽ የሕዝብ እና የአገር ጥቅም የሚያስቀድሙ ለህዝብ ጥቅም የሚያገለግሉ ብቃት ያላቸው ምሁራን በማዘጋጀት የሃገር እና የቤተክርስትያን እድገት ለማነቃቃት የሚል መሆኑ በመግለጥ፣ መንበረ ጥበቡ ከሚያካታቸው የትምህርት ዘርፎች ውስጥ ቲዮሎጊያ፣ ፍልስፍና፣ የኤኮኖሚና የስነ እድገት፣ የስነ መገናኛ ብዙኃን፣ የስነ ፖለቲካ እና የቤተ ክርስትያን ቀኖና የሚሉትን ያካተተም ጭምር መሆኑ ጠቅሰው፣ መንበረ ጥበቡ 2.200 ተማሪዎች 77 አስተማሪዎች 20 ረዳት አስተማሪዎች 63 የመንበረ ጥበቡ የመስተዳድር እና ያገልግሎት መስጫ ሠራተኞች እንዳሉትም ገልጠዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.