2017-11-28 15:30:00

የማያንማር (የቀድሞ ስሟ በርማ) አጠቃላይ ሀገራዊ ሁኔታ በአጭሩ


የማያንማር (የቀድሞ ስሟ በርማ) አጠቃላይ ሀገራዊ ሁኔታ በአጭሩ

ማያንማር እንደ የአውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር በ2015 ዓ.ም. በተደረገው የሕዝብ ቆጠራ 54.4 ሚልዮን ሕዝብ ብዛት እንዳላት የተገለጸ ሲሆን በዋና ከተማዋ ያንጎን 4,800, 000 ሺ ሰዎች ይኖራሉ። እንደ የአውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር እስከ 2005 ዓ.ም. ድረስ የያንጎን ከተማ የምያንማር ዋና ከተማ ሆና ማገልገሉዋ የሚታወቅ ሲሆን “ያንጎን” የሚለው መጠሪያ ያገኘው እንደ የአውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር 1755 ዓ.ም. በወቅቱ በሀገሪቷ ሲካሄድ የነበረ የእርስ በእርስ ጦርነትን ማብቂያን አስመልክቶ የተሰጣት ስያሜ ሲሆን ይህም በሀገሪቷ ቋንቋ  “የግጭቶች ማብቂያ” የሚል ትርጓሜ አለው። እንደ የአውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር ከ2005 ዓ.ም. ጀምሮ ኖ ፒ ቶ የሀገሪቷ ውና ከተማ በምሆን እያገለገለዝ ሲሆን በሁኑ ጊዜ የምያንማር ዋና ከተማ የሀገሪቷ መዲና ከመሆኑዋ ባሻገር ከፍተኛ የሆነ የእንዱስትሪ እና መዋለ ነዋይ የሚንቀሳቀስባት ቦታ እንደ ሆነች ይታወቃል።

አብላጫው የሀገሪቷ ሕዝብ የቡዳ እምነት ተከታይ ሲሆን ኢኮኖሚያቸው መሰረቱን ያደርገው በከፍተኛ ሁኔታ እየተመረተ በሚገኙ የሩዝ፣ የጣውላ እና የመዕድናት ምርት ላይ እንደ ሆነም ለመገንዘብ ችለናል።

በማያንማር ዋና ከተማ በያንጎን የሚገኘው የካቶሊክ ሀገረ ስብከት በይፋ የተመሰረተው እንደ አውሮፓዊያን የቀን አቆጣጠር በጥቅምት 8/1991 ዓ.ም. ሲሆን በዚሁ ርዕሰ ሰባካ (Metropolis) ውስጥ ከሚኖሩ 12,191,500 ሕዝብ ወስጥ 62,490 የካቶሊክ ምዕመናን 42 ቁምስናዎች፣ 8 ትላልቅ አብያተ ክርስቲያናት፣ 89 የሀገረ ስብከት ካህናት፣ 23 ደናግላን 47 የዘርዐ ክህነት ተማሪዎች 72 የተለያዩ ማኅበራት፣ 382 የሴቶች ገዳም አባላት፣ 23 የትምሕርት መስጫ ተቋማት፣ 18 የእርዳታ መስጫ መዕከላት ይገኝእሉ። በዚህ በያዝነው ዓመት ብቻ 1,207 ምዕመናን መጠመቃቸው ታውቁዋል። የሀገረ ስብከቱን በበላይነት የሚመሩትም የ69 አመቱ ሊቀ ጳጳሳት ካርዲናል ቻርለስ ማኡንግ ቦ ናቸው።

 

 








All the contents on this site are copyrighted ©.