2017-08-11 09:19:00

ሥነ ምህዳራዊ ቲዮሎጊያ፥ ተፈጥሮን ለመንከባከብና በሚገባ መንገድ ለመጠቀም


የሕይወት ባህል መሠረት ያደረገ የእግዚአብሔር ዱካ በፍጥረት ሁሉ ህልውናውን በመለየት ተግባራችንን ተፈጥሮ ለመጠቀም የምንከተለው ሥልት ሁሉ በጥልቀት ለመመርመር የሚያግዝ በሥነ ምህዳራዊ ቲዮሎጊያ ዙሪያ ጥልቅ አስተንትኖ ማድረግ ያለው አስፈላጊነት በሁሉም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን በምትገኝበት ክልል እየትገለጠ መሆኑ ኮምቦናዊ ካህን አባ ዳሪዮ ቦሲ በስልክ ከቫቲካን ረዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ ገልጠው፥ የአማዞንን ክልል ለመከላከል ሰው በተፈጥሮ ላይ የሚፈጽመው አመጽ በዚህ የአማዞን ክልል አበይት ኢንዳስትሪዎች ለመገንባት በሚል የተፈጥሮና የፍጥረት ጤንነት ግድ የማይሰጥ አርቆ የማይመለከት ትርፍ ማከበት ብቻ የሚል እቅድ ላይ የጸናው የሚከተሉት የኤኮኖሚ ሂደት የሚያስከትለው ሰብአዊ ማኅበራዊና ምኅዳራዊ ችግር በጥልቀት የሚያብራራ የሥነ ምኅዳር ቲዮሎጊያ ዙሪያ የሚመክር ቀዳሚ ዓውደ ጥናት እ.ኤ.አ. ነሐሴ 16ና 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በብራዚል እንዲካሄድ በእቅድ መያዙ ባካሄዱት ቃለ ምልልስ አስታውቋል።

የመላ አማዞን ቤተ ክርስቲያናዊ መረብትና የቤተ ክርስቲያንና በማዕድን ሃብት የታደሉ ክልሎች መረብት አማካኝነት ይኽ በብራዚል ሊካሄድ የተወሰነው በዓይነቱ ቀዳሚ የሆነው የሥነ ምኅዳራዊ ቲዮሎጊያ ዓውደ ጥናት ቤተ ክርስቲያን ከአገሬው ሕዝብና እንዲሁም እናት ተፈጥሮን በመንከባከብ ረገድ አብራ በመጓዝ በዚህ በአሁኑ ሰዓት የዓለም ኤኮኖሚ ቅጥ የለሽ እየሆነ በምኅዳርና በሰው ልጅ ባጠቃላይ በፍጥረት ላይ እያስከተለው ያለው ችግር ለይቶ ተፈጥሮና ሕዝብን ለመከላከል ምን መደረግ አለበት ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠትና የሥነ ምኅዳር ጥሪ ለይቶ በማብራራት ሰው የተፈጥሮ ባላባት ሳይሆን አቃቢ ተከባካቢ መሆኑ እንዲገነዘብ ለማድረግ ያለመ ዓውደ ጥናት መሆኑ አባ ቦሲ ገልጠዋ።

ዓውደ ጥናቱ ለየት ባለ መልኩም ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ይሴባሕ በሚል ርእስ ሥር በተፈጥሮና በፍጥረት ዙሪያ ሥልጣናዊ ትምህርት የሰጡበት አዋዲ መልእክት መሠረት በማድረግና ይኸንን ዓዋዲ መልእክት በጥልቀት የሚያስተነትን የክልሉ ሁኔታ የሚያገናዝብ ነው ካሉ በኋላ ከአገርየው ሕዝብ ከተለያዩ ማኅበራዊና ምኅዳራውያን እንቅስቃሴዎች ጋር በመተባበር የሚመክርና ስለ ሥነ ምኅዳራዊ ቲዮሎጊያ ጥልቅ አስተንትኖ የሚደረግበት ዓውደ ጉባኤ ይሆናል ሲሉ ያካሂዱት ቃለ ምልልስ አጠቃለዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.