2017-02-02 13:08:00

ከቫቲካም ሬዲዮ የአማሪኛ የስርጭት ክፍል የተላለፈው የረቡዕ የጥር 24/2009 ዓ.ም. ዜና።


ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በጥር 23/2009 ዓ.ም. በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ወቅት ባሰሙት ስብከት ኢየሱስ ምንም ዓይነት ታዋቂነትን ሳይሻ በመካከላችን ሁል ጊዜ እየተመላለሰ ይገኛል ማለተችው ተገለጸ።

የእዚህን ዜና ሙሉ ይዘት ከእዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ!

ዓይናችንን ያለማቋረጥ በኢየሱስ ላይ የሚያተኩር ከሆነ በሚይስደንቅ ሁኔታ እርሱም በፍቅር እንደ ሚመለከተን መገንዘብ እንችላለን በማለት ስብከታቸውን የጀመሩት ቅዱስነታቸው በእለቱ ከተነበበው ወደ ዕብራዊያን ከተጻፈው መልዕክት በመጥቀስ በጽናት ዓይናችን በኢየሱስ ላይ እንዲያተኩር ማድረግ ያስፈልጋል ካሉ ቡኋላ በወንጌል አማካይነት ኢየሱስ እኛን ይቀርባል፣ ይመለከተናልም ኢየሱስ ሁል ጊዜም ቢሆን ለእኛ ቅርብ ነው፣ በእኛ መካከልም ይመላለሳል ብለዋል።

“ኢየሱስ ሕዝቡ እንዳይነካው በማሰብ እንደ አንድ ባለ ስልጣን በጠባቂዎች ታጅቦ የሚዘዋወር አምላክ አልነበረም በማለት ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው በሕዝቦች መካከል በነፃነት በመዘዋወር በሕዝቡ ተከቦ ይኖር እንደ ነበረም ገልጸዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.