2016-12-30 17:24:00

ከቫቲካም ሬዲዮ የአማሪኛ የስርጭት ክፍል የተላለፈው የሰኞ የታኅሣሥ 21/2009 ዓ.ም. ዜና።


እንደ አውሮፓዊያኑ የቀን አቆጣጠር 2016 ዓ.ም. በመገባደድ ላይ ይገኛል። 2016 ዓ.ም. ለርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በጣም ብዙ ሥራ የበዛበት፣ 7 ሀገራትን የጎበኙበት፣ አነጋጋሪ ሆኖ ያለፈውን አሞሪስ ላይቲሲያ በአማሪኛው የፍቅር ሐሴት የተሰኘውን በቤተሰብ ዙሪያ የሚያጠነጥነውን ቃለ ምዕዳን የጻፉበት እንዲሁም ቅዱስ ልዩ የምሕረት ዓመት የተከበረበት፣ አጠቃላይ አስተህሮን ለምዕመናን ያደረጉበት፣ በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት መስዋዕተ ቅዳሴን ያሳረጉበት እና የቅድስት መንበር አጠቃላይ መዋቅር እንዲታደስ ያደረጉበት ዓመት ነው።

በተለይም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በእዚህ በመጠናቀቅ ላይ በሚገኘው የአውሮፓዊያኑ አመት ምዕመናን ሥር ነቀል የሆነ መንፈሳዊ ለውጥ እንዲያደረጉ ከፍተኛ ጥረት ያደርጉበት፣ በተለይም ቤተ ክርስቲያን ምዕመናኖቹዋ በወንጌል የሚገኘውን ደስታ በመሞላት ይህንንም ደስታ በዓለም ሁሉ ውስጥ ያዳርሱ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን ጥረት እንድታደርግም በተደጋጋሚ ጥሪ ያቀረቡበት ዓመት ነው።








All the contents on this site are copyrighted ©.