2016-11-25 13:12:00

የኅዳር 14/2009 ዓ.ም. የራዲዮ ቫቲካን የአማሪኛ ዜና


ቅዱስ አባታችን ፍራንቸስኮ በትላንትናው እለት ማለትም በኅዳር 13/2009 በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ወቅት ባሰሙት ስብከት በጌታ የምናምን ሰዎች ከሆንን ሞትን መፍራት የለብንም  ካሉ ቡኋላ ነገር ግን በፍጹም እንደ ማንሞት በመቁጠርና ሕይወታችን ተሸጋጋሪ እንዳልሆንቸ በሚያስተምር ጥራዝ ነጠቅ አስተምህሮ ላይ ከመመርኮዝ መጠንቀቅ ይግባናል ማለታቸው ተገለጽ።

በእለቱ ከዩሐንስ ራእይ በተወሰደው ምንባብ ላይ ተመርኩዘው ቅዱስነታቸው ያደረጉት ስብከት ትኩረቱን አድርጎ የነበረው ሁላችንም በመጨረሻ የፍርድ ቀን ከኢየሱስ ጋር ፊት ለፊት እንደ ምንገናኝ በሚያወሳው ጭብጥ ሐሳብ ላይ ተመርኩዞ የነበረ ሲሆን በስብከታቸውም ስለ መጨረሻ ቀን ሕይወታችን እንድናስብ ጌታ ይጠራናል ካሉ ቡኋላ ምክንያትም ሁላችንም ሙዋቾች በመሆናችን የተነሳ ነው ብለዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.