2016-03-02 08:49:00

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ለመጀመርያ ጊዜ በሮም የአራት ቀናት ጐብኝት አደረጉ።


በኢትዮጵያ  ሊቀ ጳጳሳት  ዘ አኽሱም  ወ እጨገ ተክለሃይማኖት ኦርቶዶስክ ተዋህዶ  ቤተ  ክርስትያን  ፓትርያርክ  ብጹዕ ወቅዱስ  አቡነ ማትያስ  ቀዳማዊ  ለመጀመርያ ግዜ በሮም  የአራት ቀናት  ጐብኝት አድርገዋል ።ብጹዕ ወቅዱስ  አቡነ ማትያስ  ቀዳማዊ  በሮም ቆይታቸው በቅዱስ ጰጥሮስ ካተድራል   የሐዋርያ  ቅዱስ ጰጥሮስ  መቃብር ፡  በቅድስት  መንበር  የክርስትያኖች አንድነት  ጳጳሳዊ ምክር ቤት እና   ቫቲካን እምብርት ላይ  የሚገኘው  የኢትዮጵያ  ካቶሊካዊ  ጳጳሳዊ  ኮለጅ  ጐብኝተዋል።

ኮለጁ  በጐበኙበት ግዜ  የኮለጁ ካህናት የምስራቃውያን  አብያተ ክርስትያናት ማሕበር የበላይ  ሐላፊ  ብጹዕ ካርዲናል  ለኦናርዶ ሳንድሪ   በፍረንሳይ እና  ቫቲካን  የኢትዮጵያ መንግስት   አምባሳደር  ነጋ ጸጋዪ  እና  ጥሪ  የተደረገላቸው  እንጎዶች  ደማቅ  አቀባበል አድርግውላቸዋል ።

 እንዲሁም ሮም  በሚገኘው  ኡርባንያን  ጳጳሳዊ  ኮለጅ  ውስጥ   በሚገኘው ቤተ  ጸሎት  በሮም  እና አከባቢ  የሚኖሩ  የኢትዮጵያ  ማሕበረ ሰብ  አባላት  በተገኙበት  ሥርዓተ ቅዳሴ   አሳርገዋል ።

 ዛሬ ረፋድ ላይ   በቫቲካን  ሐዋርያዊ አዳራሽ  ውስጥ  ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት  ፍራንሲስ  ጋር  ተገናኝተው  ተወያይተዋል ።

 በሮማዊት ቅድስት ካቶሊካዊት  ቤተ ክርስትያን እና  በየኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስትያን  መካከል  የቆየ   መልካም  ግንኙነት  እንዳለ   በቫቲካን የተሰጠ  መግለጫ  ጠቁሞ የቀድሞ  የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋህዶ  ቤተ ክርትያን  ፓትርያሪክ ብጹዕ ወ ቅዱስ  አቡነ ጳውሎስ  እንደ ጎርዮስ አቆጣጠር  በ1993  ቫቲካን በይፋ መገብኘታቸው እና  በወቅቱ  ከነበሩ  ነፍሰሄር ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት  ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ  መገናኘታቸው  ቀጥሎም ፡  በ2009  ይሄም ጎርዮሳዊ  የቀን  ቀመር   ከቀድሞ  ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት   በነዲክቱስ  16ኛ  ጋር  መገናኘታቸው  ጠቅሶ  በሮማዊት ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን እና  በኢዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን መካከል  መልካም ግንኙነት  እንዳለ  ዘግበዋል።

 የቀድሞ የኢትዮጵያ  ፓትርያርክ  ብፁዕ  ወቅዱስ  አቡነ ጳውሎስ ወርሀ ነሐሰ 2012 ከዚህ ዓለም  በሞት እንደተለዩ  ብጹዕ  ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  ቀዳማዊ  እንደ አውሮፓዊያን የቀን አቆጣጠር በየካቲት 28 2013 የኢትዮጵያ  ስድስተኛ  ፓትርያሪክ  በመሆን  በመንበረ ጻባዖት ቅድስት ሥላሴ ካተድራል  አዲስ አበባ ላይ  ሢመተ ፕትርክናቸው  መፈጸሙ  የሚታወስ ነው ።

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  አማርኛ  ትግርኛ  እንግልዝኛ  ግሪክኛ ኤብራይስጥኛ  እና  አረብኛ  አቀላጥፎው  እንደሚናገሩ  ይታወቃል ። ኢትዮጵያዊ  ፓትርያሪክ  ብጹዕ ወቅዱስ  አቡነ ጳውሎስ  እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በጥቅምት ወር 2009 በቫቲካን ውስጥ  ይካሄድ  ለነበረው  የአፍሪቃ ብጹዓን ጳጳሳት  ሁለተኛ  ልዩ  ሲኖዶስ  የአፍሪቃ አህጉር  ወቅታዊ  ሁኔታ  እና  የአፍሪቃ  ህዝቦች ለሚገጥምዋቸው  ፍልምያዎች  የመቋቋም  ክህሎት ትኩረት  ሰጥተው  ንግግር  እንድያደርጉ  የቀድሞ  ርእሰ ሊቃነ  ጳጳሳት በነዲክቱስ  ፓትርያሪኩን   መጋበዛቸው  በቫቲካን የተሰጠ  መግለጫ  አስገንዝበዋል።

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 








All the contents on this site are copyrighted ©.