Home Archivio
2013-11-27 16:02:29
ቅ.አ.ር.ሊ.ጳ.፦ ለግኑኝነት ባህል ታታሪ ሆኖ መገኘት
በአርጀንቲና በኢንዳስትሪው ዘርፍ የሚጠቃለሉት ሁለት አበይት የሠራተኛ ማኅበራት ጠቅላይ ዋና ጸሓፊዎችን እ.ኤ.አ. ህዳር 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በአገረ ቫቲካን በሚገኘው በቅድት ማርታ ሕንፃ በቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ አቀባበል እንደተደረገላቸው ሎ ሶርቫቶረ ሮማኖ የተሰየመው የቅድስት መንበር ዕለታዊ ጋዜጣ ሲያመለክት፣ ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. የሠራተኛ ማኅበራት ጠቅላይ ዋና ጸሓፊዎችን ተቀብለውም ሁሉም ለግኑኝነትና ለሰላም ባህል ተግቶ እንዲሠራ በማሳሰብ ለዚህ ባህል ታታሪ ሆኖው እንዲገኙም አደራ በማለት እ.ኤ.አ. በ 2000 ዓ.ም. ገና የቦነስ አይረስ ሊቀ ጳጳሳት እያሉ በከተማይቱ በአደባባይ ደ ማዮ የተከተሉት የወይራ ዛፍ ትርጉሙም ግኑኝነትና የስላም ባህል ማስፋፋት የሚልና አርማነቱንም በእሳቸው ብፁዕ ካርዲናል እያሉ ለዓለም አቀፍ የመላ ትምህርት ቤቶች ድረ ግኑኝነት በማቋቋም ሁሉም ለግኑኝነትና ለስላም ባህል እንዲተጋ ከትምህርት ቤቶች ጀምሮ ለመልካም ዓላማ ማነጽ ያለው አስፈላጊነት እንዳስፋፋ ሎ ሶርቫቶረ ሮማኖ ዕለታዊ ጋዜጣ በማስታወስ የዚሁ ማኅበር ድረ ገጽ አድራሻም
www.scholasoccurrentes.org
የሚል መሆኑ ይጠቁማል።
All the contents on this site are copyrighted ©.