2013-09-27 16:03:21

የቦርጎሊዮ ዝርዝር


RealAudioMP3 እ.ኤ.አ. ጥቅምት ወር 2013 ዓ.ም. አቨኒረ ለተሰየመው የኢጣሊያ ብፁዓን ጳጳሳት ምክር ቤት ዕለታዊ ጋዜጣ ዘጋቢና ጋዜጠኛ ነሎ ስካቮ የቦርጎሊያ ዝርዝር በሚል ርእስ ስር ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ በአርጀንቲና የነበረው ወታደራዊ አምባገነን ፈላጭ ቆራጭ መንሥት ያካሂደው ከነበረው በጠቅላላ 30 ሺሕ የአገሪቱ ዜጎች ለሞት የዳርገው ሽብር ይጋለጡ የነበሩት ብዙ የአገሪቱ ዜጎችን ለማዳን ያካሂዱት ስውር የሚሰዋ የፍቅር ተግባርና አገልግሎት ጠለቅ ባለ ሁነት በተለያዩ ቤተ መዛግብት ጥልቅና ልዩ ጥናት በማካሄድ የደረሱት ሰነዳዊ መጽሓፍ ለንባብ እንደሚቀርብ የቅድስት መንበር መግለጫ ሲያመለክት፣ ደራሲው ጋዜጠኛ ነሎ ስካቮ ከቫቲካን ረዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ፦ ካካሄዱት ጥናት ያገኙት የቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. ተክለ ሰውነት በነበረው የአርጀንቲና ወታደራዊ አምባገነን መንግሥት ሳይታወቁ ለሞት ተላልፈው ይሰጣሉ የሚባሉትን የአገሪቱ ዜጎች ለይተው ለማወቅ በስውር የነበረው የአንባገነን መንግሥት የጸጥታና ደህንነት የስላላ አባላት ከሆኑት ውስጥ አንዳንዱን በቅርብ በማወቅ መረጃ በማግኘት ይገደላሉ የሚባሉትን በመለየት ከሞት አደጋ እንዲተርፉ ማድረጋቸው የሚመሰክር ነው። ይኽ ደግሞ በተለያዩ ሰነዶች ውስጥ ተዘግቦ የሚገኝ እውነት ነው ሲሉ የሰጡትን ቃለ ምልልስ እዚህ ላይ አጠቃለዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.