2011-05-20 14:17:01

ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. በትውልድ አገራቸው ጀርመን


ቅዱስ አባታችን ር.ሊ.ጳ. በትውልድ አገራቸው ጀርመን እፊታችን መስከረም ወር 2011 ዓ.ም. ይፋዊ እና ሐዋርያዊ ጉብኝት በማካሄድ በሚፈጽሙት መንፈሳዊ እና ባህላዊ መርሃ ግብሮች ለመሳተፍ የሚጠይቀው የምእመን RealAudioMP3 እና የሥነ ባህል ሊቃውንት ብዛት እጅግ ከፍ እያለ መምጣቱ ይኸንን ሐዋርያዊ ጉብኝት ማእከል በማድረግ ስለ ጉዳዩ የተለያዩ መግለጫዎች የሚሰራጭበት ድረ ገጽ በጠቅላላ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ 28 ሺህ ሕዝብ መመዝገቡ ሲር የዜና አገልግሎት ድረ ገጹ ጠቀስ ያሰራጨው የዜና ምንጭ አስታወቀ።

ቅዱስ አባታችን በጀርመን ሐዋርያዊ ጉብኝት በማካሄድ በርሊን እ.ኤ.አ መስከረም 22 ቀን 2011 ዓ.ም. በሚያሳርጉት መሥዋዕተ ቅዳሴ መስከረም 23 ቀን በሚመሩት ጸሎት ሰርክ፣ እንዲሁም መስከረም 24 በኤርፉርት በሚመሩት መሥዋዕተ ቅዳሴ በመጨረሻም መስከረም 25 ቀን 2011 ዓ.ም. በፍሪበርግ በሚመሩት የመልአከ እግዚአብሔር ጸሎት ለመሳተፍ የሚጠይቀው የምእመናን ብዛት ከቀን ወደ ቀን ከፍ እያለ መምጣቱ የጀርመን ብፁዓን ጳጳሳት ምክር ቤት የሰጠው መግለጫ የጠቀሰ ሲር የዜና አገልግሎት አመለከተ።







All the contents on this site are copyrighted ©.