2010-10-07 16:01:37

ቅዱስ ኣባታችን የመካከለኛው ምሥራቅ የጳጳሳት ሲኖዶስ አባላት ሰይመዋል


እ.አ.አ ከጥቅምት 10 ቀን እስከ 24 2010 ዓ.ም. ‘ካቶሊካዊት ቤተ ክርስትያን በመሀከለኛው ምሥራቅ፤ “ኅብረትና ምስክርነት፤ ኣማኞች ሁሉ ኣንድ ልብና ኣንድ ኣሳብ ነበራቸው’ (ግ.ሐ 4፡32)” በሚል መሪ ሓሳብ ሊካሄድ በተዘጋጀው የመካከለኛው ምሥራቅ የጳጳሳት ሲኖዶስ የሚሳተፉ ልዩ ኣባላትን ሰይመዋል፤ እነርሱም፤

    የካርዲናላት ድርገት ሓላፊ ብጹዕ ካርዲናል ኣንጀሎ ሶዳኖ

    የኪቭሃልይ ከፍተኛ ሊቀጳጳስና የኡክራይን የእስቱዲቲ መነኮሳን ኣባል ብጹዕ ካርዲናል ሉብሚር ሁሳር

    የክርስትያን ኣንድነት ጳጳሳዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር የነበሩ ብጹዕ ካርዲናል ቫልተር ካስፐር

    በኢየሩሳሌም በቅዱስ መቃብር የኤኰስትረ ማኅበር ከፍተኛ መምህር ብጹዕ ካርዲናል ፓትሪክ ፎሊ

    የኢየሩሳሌም ላቲናዊ ሥርዓት ልሂቀ ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ ኣቡነ ሚሸል ሰባህ

    የትሪቫንድሩም ሲሮ ማላንካረሲ ከፍተኛ ሊቀ ጳጳሳት ብጹዕ ኣቡነ ባሲልዮስ ክሊሚስ

    የቢብሎ ሥዩመ ሊቀ ጳጳስና ሓዋርያዊ እንደራሴ ብጹዕ ኣቡነ እድሞንድ ፋርሃት

    የኣረዞ ኮርቶና ቅዱስ መቃብር ሥዩመ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ ኣቡነ ሪካርዶ ፎንታና

    የዳርኒ ሥዩመ ሊቀ ጳጳስና የሊባኖስ ሓዋርያዊ እንደራሴ ብጹዕ ኣቡነ ሙንገድ ኤል ኣሸም

    የሊብያ ቶለማይደ ሥዩመ ሊቀ ጳጳስና የምሥራቃውያን ኣብያተ ክርትያን ማኅበር ጸሓፊ ብጹዕ ኣቡነ ሲሪል ቫሲል

    የኦራድያ ባሕር ጳጳስ ብጹዕ ኣቡነ ቪርጂል በርሰያ

    የካርካብያ ሥዩመ ጳጳስና በግሪክ የሚገኙ የቢዛንቲን ሥርዓተ ኣምልኮ ካቶሊካውያን ኤዛርቃ ብጹዕ ኣቡነ ዲመጥርዮስ ሳላካስ

    የፎራስያን ሥዩመ ጳጳስና የኤርናኩላም ኣንጋማልይ ሲሮ ማላባረሲ ጉባኤ ጳጳስ ብጹዕ ኣቡነ ቦስኮ ፑቱር

    የቅርቡ ምሥራቅ ካቶሊካዊ ግብረ ሠናይ ማኅበር ዋና ጸሓፊ ብጹዕ ኣርከማንድሪታ ሮበርት እስተርን

    በሊባኖን የብዞማር ፓትርያርካዊ ቤተ ክህነት ተቅዋም ኅየንተ ብጹዕ ኣቡነ ሚካእል ኣንትዋን ሙራድያን

    በኢየሩሳሌም ላቲናዊ ሥር ዓተ ኣምልኮ የዕብራይስጥ ቋንቋ የሚገልግሉ ካቶሊካውያን ቆሞስ ጥቀ ክቡት ኣባ ዳዊት ነሃውስ ናቸው።


ቅዱስነታቸው ስማቸውን እላይ የተጠቀሱትን ከሰየሙ በኋላ የጳጳሳቱ ሲኖዶስ ያቀረበውን የሊቃውንት ሌሎች በሲኖዶሱ የሚካፈሉ ኣስፈላጊ ሰዎች ስም ዝርዝር ማጽደቃቸውን ከቅድስት መንበር የመጣ ዜና ኣመልክተዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.