2010-07-09 15:01:00

የእውነተኛው እምነት እውነተኛ ምስክር


በቻይን በሄ በኡ አውራጃ ለዝሄንግዲን ሰበካ ሕጋዊ ሊቀ ጳጳስ ነገር ግን ይህ የእንተ ላእለ ኵሉ ቤተ ርክስትያን ሥር የተሰጣቸው ኃላፊነት በቻይና ገና ይፋዊ እውቅና ያላገኘ፣ 75 ዓመት እድሜ ያላቸው በቻይና ለምትገኘው ካቶሊክ ቤተ RealAudioMP3 ክርስትያን ካህናት እና ብፁዓን ጳጳሳት አብነት የእውነተኛው እረኛ አፍቃሪ እና እርሱን በመምሰል በቻይና ያለው ሃይማኖታዊ ፖለቲካዊ እና ሰብአዊ ጉዳይ በተመለከተ አስተያየት የሚሰጡ ስለ እምነት እና ስለ ፖለቲካ ጉዳይም በተመለከተ ግልጽ የሆነ ውሳኔ ያላቸው እና ይኽንን ይፋ ከማድረግ ያልተቆጠቡ ብፁዕ አቡነ ጁሊዮ ዚያ ዚግዎ እ.ኤ.አ. መጋቢት 31 ቀን 2009 ዓ.ም. እዚህ በቅድስት መንበር በቻይና ስላለቸው ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን ጉዳይ በተመለከተ ይኽንን ጉዳይ የሚከታተለው ድርገት ይፋዊ ስብሰባው በከፈተበት ዕለት በቻይና መንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት እጅ ተይዘው ለእስር የተዳረጉት ከትላትና በስትያን ነጻ መለቀቃቸው ፊደስ የዜና አገልግሎት አስታወቀ።

ብፁዕ አቡነ ጁሊዮ ዢያ ዚጉዎ እ.ኤ.አ. ግንቦት 1 ቀን 1935 ዓ.ም. የተወለዱ እ.ኤ.አ. ሰኔ 7 ቀን 1980 ዓ.ም. ማዕርገ ክህነት ተቀብለው እ.ኤ.አ. የካቲት 8 ቀን 1981 ዓ.ም. የዘንግዲንግ ሰበካ ሊቀ ጳጳስ እንዲሆኑ መሾማቸው የቅድስት መንበር መግለጫ ይጠቁማል።







All the contents on this site are copyrighted ©.