2010-04-14 14:10:49

የፍትሃት ቅዳሴ፣ በስሞሎንስኪ በአይሮፕላን አደጋ ምክንያት ለሞቱት


የካቶሊክ ትምህርት የሚንከባከበው ቅዱስ ማህበር ኅየንተ ብፁዕ ካርዲናል ዜኖን ግሮቾለውስኪ የመሩት የዓለማውያን ምእመናን ጉዳይ የሚከታተለው ጳጳሳዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር ብፁዕ ካርዲናል ስታኒስላው ርይልኮ፣ RealAudioMP3 ጳጳሳዊ የጤና ጉዳይ ተንከባካቢ ምክር ቤት ሊቅ መንበር ብፁዕ አቡነ ዝይግሙንት ዞሞውስኪ እና ዋና ጸሓፊያቸው ብፁዕ አቡነ ኾሴ ልዊስ ማርኪተ ሬድራዶ እና ዓለም አቀፍ የቅዱስ ቁርባን ጉባኤ አስፈጻሚ ጳጳሳዊ ኮሚቴ ሊቀ መንበር ብፁዕ አቡነ ፒየሮ ማሪኒ እና ከመቶ በላይ የሚገመቱ ካህናት የተሳተፉበት በቅድስት መንበር የፖላንድ ልኡከ መንግሥት ሃና ሱቾካ እና ሌሎች ልኡካነ መንግሥታት የተሳተፉበት በአይሮፕላን አደጋ ሳቢያ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩ ለፖላንድ ርእሰ ብሔር ሌኽ ካዝይንስኪ እና ለክብርት ባለ ቤታቸው ማሪያ እና ሌሎች የአደጋው ሰለባ ለሆኑት ትላንትና ሮማ በሚገኘው በቅዱስ መንፈስ ዘ ሳሲያ የፍትሃት ቅዳሴ መቅረቡ ተገለጠ።

የደረሰው አሰቃቂው አደጋ በማስመልከትም ብፁዕ አቡነ ዝይግሙንት ዚሞውስኪ ከቫቲካን ሬዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ፣ ሞታችንን ሞቶ ከሞት እርዛት ነጻ ያወጣን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለፖላንድ ህዝብ፣ ለሟቾች ቤተ ሰብ ማጽናናቱን ይሰጥ ዘንድ እና ለሞት አደጋ የተጋለጡትም እግዚአብሔር በመንግሥቱ ይቀበላቸው ዘንድ መጸለዩንም ገልጠው፣ ሁላችን የትንስኤውን እምነት ካለ ማመንታት መኖር ይገባናል፣ ይህች የር.ሊ.ጳ. የእግዚአብሔር አገልጋይ ዮሐንስ ጳውሎስ ዳግማዊ አገር እግዚአብሔር ይባርካት በማለት የሰጡትን ቃለ ምልልስ ደምድመዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.