2010-02-17 14:14:10

27ኛው ዓለም አቀፍ ዕለተ ህሙማን


ባለፈው ዓርብ የሕክምና ባለ ሙያዎች ሓዋርያዊ ግብረ ኖልዎ የሚንከባከበው ጳጳሳዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር ብፁዕ አቡነ ዝይግሙንት ዞሞውስኪ ዓለም ዓቀፍ የህሙማን እለት ምክንያት በማድረግ፣ በዋና ጸሓፊዎቻቸው RealAudioMP3 ብፁዕ አቡነ ኾሰ ረድራዶ እና በብፁዕ አቡነ ማሪኡስዝ ጊየርስ ታጅበው ሮማ ከተማ የሚገኘውን ቅዱስ መንፈስ የሕክምና መስጫ ማእከል መጎብኘታቸው ሲገለጥ፣ የሮማ የጤና ጥበቃ ጽ/ቤት አስተዳዳሪ ሓኪም ማውሮ ጎለቲ ጉብኝቱ ብፁዓን አቡናት በሆስፒታሉ ተገኝተው የህክምናው ማእከል ያለውን የሕክምና መስጫ ክፍሎች በመዘዋወር ብቃቱን የሚያስመሰክር በዕደ ጥበብ የተካነ ዘርፎችንም በመጎብኘት፣ በሆስፒታሉ የሚገኙትን ህሙማን በመጠየቅ እና አብሮ በመጸለይ የተከናወነ መሆኑ በመግለጥ፣ የሕክምና ሙያ ቴክኒካዊ ብቃት የሚያረጋገጠው ብቻ ሳይሆን ጥሪም ጭምር መሆኑ ብፁዕ አቡነ ዚሞውስኪ ሆስፒታሉን በመጎብኘት ለህክምና ባለ ሙያዎች ባሰሙት መልእክት ማሳሰባቸው ሓኪም ማውሮ ጎለቲ አስታውቀዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.