Home Archivio
2009-08-21 14:16:24
ኒጀር
እ.ኤ.አ. ከ 1999 ዓ.ም. ጀምረው የኒጀር ርእሰ ብሔር በመሆን በሥልጣን ላይ የሚገኙት ማማዱ ታንድጃ የርእሰ ብሄር ሥልጣናቸውን እ.ኤ.አ. ታህሳስ 22 ቀን 2009 ዓ.ም. በማገባደድ ዳግም ለሶስተኛ ጊዜ ርእሰ ብሔር ለመሆን
በእጩነት ለምርጫ ለመቅረብ የአገሪቱ ሕገ መንግሥት የማይፈቅድላቸው ሆኖ እያለ ይኸንን ሕግ በሌላ ሕግ ለመሻር እርሱም ተልእኮአቸ ገደብ አልቦ ለማድረግ የሚፈቅድ ሕገ ንድፍ በሕገ መንግሥት ለማከል ጥረት እያደረጉ ናቸው። ይህ ውሳኔ በህዝብ እንዲበየን ማድረጋቸው ሲገለጥ፣ ውሳኔው የመምረጥ መብት ካለው ህዝብ ውስጥ በ 92 በመቶ መደገፉ ተገልጠዋል።
ተቃዋሚተቃውሞ የፖለቲካ ሰልፍ ርእሰ ብሔሩ የጀመሩት የሕገ መንግሥት ህዳሴ ላንዲት አገር ዴሞክራሲያዊ ሂደት አደገኛ ነው በማለት እንደማይደገፈው ሲያስታውቅ፣ ትላትና ያገሪቱ የመንግሥት ረድዮ ጥቅምት 20 ቀን 2009 ዓ.ም. ሕዝባዊ ምርጫ እንደሚሄድ አስታውቀዋል።
All the contents on this site are copyrighted ©.