Home Archivio
2009-08-19 13:48:29
ሩሲያ
በሩሲያ ምዕራባዊ ሳይበሪያ በምትገኘው በክሃካሲያ ከተማ የሚገኘው ባይነቱ በሩሲያ ትልቅ በሆነው ባንድ የውሃ ኃይል ምንጭ ማእከል በደረሰው አደጋ ሳቢያ 12 ሠራተኞች ሕይወታቸው እንዳጡ ሲገለጥ ሌሎች
64 የማእከሉ ሠራተኞች ገና በመፈለግ ላይ መሆናቸው ይነገራል። የተሰወሩት 64 ሠራተኞች ፍለጋ እየቀጠለ ሲሆን፣ የደረሰው አደጋ ቢያንስ የሶስት ሚሊያርድ ዶላር ኪሳራ ሲገመት፣ ይህ በዓነቱ በዓለም አቀፍ ደረጃም በትልቅነቱ አራተኛ ነው ተብሎ የሚነገርለት የውኃ ኃይል ምንጭ መልሶ ላገልግሎት እንዲውል ለማድረግ ቢያንስ አራት ዓመት እንደሚፈጅ የሙያ ሊቃውንት ይናገራሉ።
All the contents on this site are copyrighted ©.