2009-08-17 14:42:02

ኢራን


በኢራን የርእሰ ብሄር አህመዲነጃድ ዳግም መመረጥ ያረጋገጠው ሕዝባዊ ምርጫ የተጭበረበረ ነው በማለት ባገሪቱ የተለያዩ የሰላማዊ ሰልፍ አድማ መካሄዱ የሚዘከር ሲሆን፣ የተካሄዱትን ሰላማዊ ሰልፎችን ለመበተን እና RealAudioMP3 ለመቆጣጠር ተሰማርቶ ከነበረው ያገሪቱ የጸጥታ ኃይሎች ጋር አቢይ ግጭት ተፈጥሮ እንደነበርና በብጥብጡ ምክንያት ተለይተው በጸጥታው ኃይል በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ያገሪቱ እውና የውጭ አገር ዜጎች ውስጥ 28 እስረኞች የሚመለከተው የፍርድ ቤት ችሎት መከፈቱ ተገለጠ። ይህ በንዲህ እንዳለ ርእሰ ብሔር አህመዲነጃድ በመንግሥታቸው ሁለት ሴቶች በሚኒስትርነት ሥልጣን እንደሚሾሙ በመግለጥ እነርሱም የጥበቃ እና የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒ. ፋታሜህ አጆርሉ እና የጤና ጥበቃ ሚኒ. ሀርዛያህ ቫሂድ ዳስትጀርዲ መሆናቸው ያስታወቁ ሲሆን፣ በኢራን እስላማዊት ሬፓብሊክ አገር ምሥረታ ወዲህ በኢራን ሴቶች በሚስትርነ ሥልጣን ሲሾሙ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑም ተገልጠዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.