2009-07-16 08:42:41

ኩባ


በኩባ የሬግላ ማሪያማዊ ቅዱስ ሥፍራ እ.ኤ.አ. ከ 1997 ዓ.ም. አስተዳዳሪ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት 74 ዓመት ዕድሜ የነበራቸው አባ አሮዮ መሪኖ ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸው የኩባ ቤተ ክርስትያን የተላለፈ ዜና አስታውቀዋል። RealAudioMP3

የኩባ ብፁዓን ጳጳስት ጉባኤ ቃል አቀባይ የሰጡትን መግለጫ ኣባ መሪኖ ለእረፍት ወደ ስፐይን ለመሄድ በመዘጋጀት ላይ እንደነበሩ ሲያስታውቅ፣ የኩባ ሕዝብ ያለው የሃይማኖት ባህል እግምት ውስጥ ያስገባ፣ ሓዋርያዊ ኖልዎ በመከተል ይሰጡት በነበረ መንፈሳዊ ማኅበራዊ እና ሰብአዊ አገልግሎት በምእመናን እና በሕዝብ ዘንድ እጅግ እተወደዱ እንደነበርም ቃለ አቀባዩ የሰጡት መግለጫ ይጠቁማል።

ይህ በንዲህ እንዳለ ባለፈው የካቲት ወር ኣባ ደ ላ ፉወንተ በኩባ ርእሰ ከተማ መገደላቸው የሚዘከር ሲሆን፣ ሁለቱ ካህናት የስፐይን ዜጎች መሆናቸውም የኩባ ብፁዓን ጳጳሳት ጉባኤ ቃል አቀባይ ኤሊዛርዶ ሳንቸስ መግለጣቸው ያሳወቀው አንሳ የዜና አገልግሎት በማሳወቅ ሁለት ሰዎች የአባ ደ ላ ፉወንት ቅትለት ተጠያቂ ናቸው በሚል ጥርጠራም ለምርመራ በቁጥጥር ሥር ማዋላቸው የዜና ምንጩ አክሎ አስታውቀዋል።








All the contents on this site are copyrighted ©.