Home Archivio
2009-07-11 08:25:00
ኢራቅ
ከትላትና በስትያና ምሽት እና እስከ ትላትና ጧት ባለው የጊዜ ገደም ውስጥ በኢራቅ ሳርድ ሲትይ በሚገኘው ዓቢያ የገበያ ሥፍራ ሁለት የተጠመዱ ቦምቦች ፍዳታ ሳቢያ 7 ሰዎች ለሞት ሌሎች 25 ደግሞ ለመቁሰል አደጋ መጋለጣቸው ሲነገር፣
ባንድ በተጣለው የፍንዳታ አደጋ ሳቢያ የኢራቅ ማእከላዊ ባንክ ቤት አስተዳዳሪ ሲናን አል ሲቢቢ የመቁሰል አደጋ እንደደረሰባቸው ከኢራቅ የተሰራጩ ዜናዎች ያመለክታሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለም በኢራቅ ሰሜናዊ ምዕራብ ክልል በምትገኘው ታል አፋር በመባል በምትጠራው ከተማ በተጣለው ያጥፍተጥ ጥፋ አደጋ ሳቢያ 14 ሰዎች ለሞት 33 ሰዎች ደግሞ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።
All the contents on this site are copyrighted ©.