Home Archivio
2009-06-17 17:18:20
ስደተኛው ኦርቶዶክስ ምእመናን ለመንከባከብ
በተለያዩ አገሮች በስደት የሚኖሩት የኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስትያናት ምእመናን የሚመራ ስደተኞች የኦርቶዶክስ ምእመናን የሚንከባከብ ኦርቶዶክሳዊ ጳጳሳዊ ጉባኤ እንዲቋቋም እ.ኤ.አ. በዚህ በያዝነው ዓመት ሊካሄድ ተውስኖ ባለው የመላ ኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስትያናት ሶኖዶስ ቅድመ ዝግጅት ምክንያት በጀነቭ ሳበዝይ ከተማ በተካሄዱት ስብሰባዎች መወሰኑ ኤሺያን ኔውስ የዜና አገልግሎት ካሰራጨው የዜና ምንጭ ለመረዳት ተችለዋል።
ይህ የኦርቶዶክስ ስደተኛው ምእመናን በሚገኝበት አገር የሚንከባከበው ኦርቶዶክሳዊ ጳጳሳዊ ጉባኤዎችን ባንድነት የሚያሰባስበው ጉባኤ ከጉባኤውቹ ሊቀ መንበርት ውስጥ የእድሜ ባለ ጸጋ በሆኑት የሚመራ እንደሚሆንም የዜና ምንጭ አክሎ አስታውቀዋል። ይህ የስደተኞች ጉዳይ የሚክታተለው ስደተኞች የኦርቶዶክስ አቢያተ ክርስትያን ምእመናን የሚከታተለው ምክር ቤት የምእመናን መንፈሳዊ ሕንጸት የሚደግፍና ምእመናኑ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስትያን መሪ ትምህርት እንዲከተል የሚያነቃቃና ቀርቦም ስለ ቤተክርስትያኑ እንዲያውቅ የሚያግዘው ማስታወቂያዎች ጭምር የሚያገኝበት እንደሚሆንም ተገልጠዋል።
All the contents on this site are copyrighted ©.