Home Archivio
2009-06-05 16:26:42
ር.ሊ.ጳ የሕፃናት መብት እንዲረጋገጥ ተማጠኑ
ቅ.ኣ.ር.ሊ.ጳ በነዲክቶስ 16 ትናንት በቅ. መንበሩ ዋና ጸሓፊ በብፁዕ ካርዲናል ታርቺዝዮ በርቶነ በኩል የተባበሩት መንግሥታት ጽሕፈት ቤት ስለ ሕፃናት መብት መክበርና መተግበር ያጸደቀውን ዉል ገቢራውነት የሚደግፍና የሚያበረታታ መልእክት ስለ ሕፃናት መብት ጉዳይ ለመሞከት ጀነቭ ላይ ለተቀመጠው ጉባኤ መልእክት መላካቸው ተመለከተ።
ቅዱስነታቸው የተባበሩት መንግሥታት ጽሕፈት ቤት ስለ ሕፃናት መብት ያጸደቀው ውል በሙሉ በአስቸኳይ ገቢራዊ መሆን እንዳለበት ያሳሰቡበት መልእክት ስለ ሕፃናት መብት ጉዳይ ለመሞከር በጀነቭ ለተቀመጠው ጉባኤ ያነበቡት ሊቀ ጳጳሳት ሲልቫኖ ማርያ ቶማሲ ናቸው።
All the contents on this site are copyrighted ©.