Home Archivio
2009-05-19 07:16:32
‘‘ቅድስት መሬት የእግዚአብሔር ፍቅር ምልክት ናት’’ ቅ.አ.ር.ሊ.ጳ በንግሥተ ሰማያት ጸሎት
ቅ.አ.ር.ሊ.ጳ ባለፈው እሁድ የንግሥተ ሰማያት ጸሎት ከመድገማቸው በፊት በቅርቡ ስለጐበኙት ቅድስት መሬት እንዲሁም የስሪላንካ የወቅቱ ሁኔታን በማስታወስ መልእክት አስተላልፈዋል።
ቅዱስነታቸው ባለፈው ሳምንት ወደ ቅድስት መሪተት ስላደረጉት መንፈሳዊ ሓዋርያዊ ጉዞ በሰፊው ነገ ሮብ ሳምንታዊው አጠቃላይ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ በሚሰጡበት ጊዜ እንደሚገልጹ አሳስበዋል። እግዚአብሔር ይህንን ትልቅ ሓዋርያዊ ጉዞ ለመፈጸም ስላስቻላቸው እንዲሁም ግብኝቱ እንዲሳካ ለተባበሩት የቅድስት መሬት፣ የቤተ ክርስትያንና የመንግሥት ባለሥልጣን የጸጥታ ኃይሎችንና በጸሎት ለሸኙዋቸው ምእመናን አመስግነዋል።
የቅድስት መሬቱ ሓዋርያዊ ጉብኝታቸው እዛ ለሚኖሩት ክርስትያን ግብረ ተልእኮ ለመፈጸም፣ ለክርስትያን አንድነት ሂደት የድጋፍ አገልግሎት ለመስጠት፣ ከአይሁድና እስላም ጋር ለሚደረጉ ውይይቶች ለማበረታታት እና ለሰላም ግንባታ እርዳታ ለመስጠን ያለመ መኖሩን አስታውቀዋል።
All the contents on this site are copyrighted ©.